settings icon
share icon
ጥያቄ፤

ክርስቲያኖች የብሉይ ኪዳንን ህግ መታዘዝ ይኖርባቸዋል?

መልስ፤


ይህንን የመረዳቱ አቢይ ጉዳይ የብሉይ ኪዳን ህግ የተሰጠው ለክርስቲያኖች ሳይሆን ለእስራኤል ነገድ እንደሆነ ያን ማወቁ ነው፡፡ የተወሰኑቱ ህጎች እስራኤላውያን እንዴት መታዘዝ እና እግዚአብሔርን ማስደሰት እንዳለባቸው ለእነርሱ ለመግለጥ ነበር (ለምሳሌ አሥርቱ ትዕዛዛት)፡፡ ከህጎቹ የተወሰኑቱ እስራኤላውያን እንዴት እግዚአብሔርን እንደሚያመልኩ እና ከኃጥአት እንደሚነጹ ለማሳየት ነበር(የመስዋዕት ሥርዓት)፡፡ የተወሰኑቱ ህጎች እስራኤላውያንን ከሌሎች ነገዶች የተለዩ ለማድረግ የታሰቡ ነበሩ (የምግብ እና የአለባበስ ህግጋት)፡፡ ዛሬ አንዳች የብሉይ ኪዳን ህግ በእኛ ላይ የጸና አይደለም፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሞተበት ጊዜ ለብሉይ ኪዳን ህግ ፍጻሜን አደረገ (ወደ ሮሜ ሰዎች 10፤4፤ወደ ገላቲያ ሰዎች 3፤23-25፤ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፤15)

በብሉይ ኪዳን ህግ ምትክ እኛ በክርስቶስ ህግ ሥር ነን (ወደ ገላቲያ ሰዎች 6፤2) ያም “ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም መውደድ እና ባልንጀራህን እንደ ራስህ መውደድ የምለው ነው” (የማቴዎስ ወንጌል 22፤37-38)፡፡ እነዚያን ሁለቱን ትዕዛዛት ብንታዘዝ ክርስቶስ ከእኛ የሚፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ እየፈጸምን ነው ማለት ነው፤ “በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።” (የማቴዎስ ወንጌል 22፤40)፡፡ አሁን ዛሬ የብሉይ ኪዳን ህግ አላስፈላጊ ነው ማለት አይደለም፡፡ ብዙዎቹ በብሉይ ኪዳን ውስጥ ያሉ ትዕዛዛት “እግዚአብሔርን መውደድ” እና “ባልንጀራህን መውደድ” በሚሉት ክፍሎች ውስጥ ይመደባል፡፡ የብሉይ ኪዳን ህግ እንዴት እግዚአብሔርን መውደድ እና ባልንጀራህን መውደዱ ምን እንደሆነ ለማወቅ ጥሩ መመሪያ ሊሆን ይችላል፡፡ በተመሳሳይም የብሉይ ኪዳን ህግ ለዛሬ ዘመን ክርስቲያኖች ይሠራል ማለት ስህተት ነው፡፡ የብሉይ ኪዳን ህግ መለኪያ ነው (የያዕቆብ መልዕክት 2፤10)፡፡ ሁሉም ይሥሩ ወይም አንዳቸውም አይሥሩ፡፡ ክርስቶስ የተወሰኑቱን የተወሰኑትን ነገሮቹን ከፈጸመ እነዚያም ፤የመስዋዕት ሥርዓት፤ ሁሉንም እሱ ፈጽሞታ፡፡

“ትዕዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነው፡፡ ትዕዛዛቶቹም ከባዶች አይደሉም” (1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፤3)፡፡ በመሠረቱ አሥርቱ ትዕዛዛት አጠቃላይ የብሉይ ኪዳን ህግ ማጠቃለያ ነበር፡፡ ከአሥርቱ ትዕዛዛት ዘጠኙ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በግልጽ ተደግመዋል (ሁሉም የሰንበትን ቀን ለመመልከት ካለው ትዕዛዝ በስተቀር)፡፡ በእርግጠኝነት እኛ እግዚአብሔርን እየወደድን ከሆነ የውሸት አማልክቶችን የምናመልክ ወይም በጣኦቶች ፊት የምንሰግድ አንሆንም፡፡ ባልንጀሮቻችንን እየወደድን ከሆነ አንገድላቸውም፤አንዋሻቸውም፤በእነሱ ላይ አናመነዝርም ወይም የእነሱ የሆነውን ነገር አንመኝም፡፡ የብሉይ ኪዳን ህግ ዓላማ እኛ ሰዎች ህግን መጠበቅ አለመቻላችንን ለመውቀስ እና ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አዳኝ መፈለጋችንን ያመለክተናል (ወደ ሮሜ ሰዎች 7፤7-9)፡፡ የብሉይ ኪዳን ህግ ለሁሉም ሰዎች ለሁልጊዜ የሚሆን ህግ እንዲሆን ፈጽሞ በእግዚአብሔር ታስቦ አያውቅም፡፡ እኛ እግዚአብሔርን እና ባልንጀሮቻችንን ልንወድ ይገባል፡፡ እነዚያን ሁለቱን ትዕዛዛት በታማኝነት ብንታዘዝ እግዚአብሔር ከእኛ የሚፈልጋቸውን ሁሉ እንጠብቃለን፡፡

English



ወደ አማርኛ መነሻ ገጽ ለመመለስ

ክርስቲያኖች የብሉይ ኪዳንን ህግ መታዘዝ ይኖርባቸዋል?
© Copyright Got Questions Ministries